የሀገር ውስጥ ዜና

ከ100 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያላቸው ለባቡር መንገድ ሥራ የሚውሉ ዕቃዎች ተያዙ

By ዮሐንስ ደርበው

October 03, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ100 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያላቸው ለባቡር መንገድ ሥራ የሚውሉ ዕቃዎች በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወሩ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አስታወቀ።

የሚመለከታቸው የክልልና የፌደራል መንግሥታት ንብረቶቹን በአግባቡ ሊያስጠብቁ ባለመቻላቸው በአካባቢው ለሚፈጠሩ ጸቦች ሰበብ እየሆነብኝ ነው ብሏል ፖሊስ፡፡