የሀገር ውስጥ ዜና

ኢጋድ በቀጠናው ሰላም እና ደህንነትን ለማረጋገጥ ለሚያደርገው ጥረት አባል ሀገራቱ ያላቸውን ድጋፍ ሊያጠናክሩ ይገባል – አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ

By ዮሐንስ ደርበው

October 03, 2022

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 23 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) አባል ሀገራት ድርጅቱ በቀጠናው ሰላም እና ደህንነትን ለማረጋገጥ ለሚያደርገው ጥረት ያላቸውን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቀረቡ፡፡

40ኛው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት አምባሳደሮች ኮሚቴ ስብሰባ በጅቡቲ ተካሂዷል፡፡