የሀገር ውስጥ ዜና

ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት እኛ ሚናችንን ልንወጣ ይገባል – የሀገር ሽማግሌዎች

By ዮሐንስ ደርበው

October 03, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀገራዊ ምክክሩ ውጤታማ እንዲሆን የሚጠበቅብንን ሚና በአግባቡ ልንወጣ ይገባል ሲሉ የሀገር ሽማግሌዎች ተናገሩ፡፡

የወላይታ እና የጋሞ አባቶች አዳነ አይዛ እና አቶ ተዘራ ሸዋዬ ÷ ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ስኬታማ እዲሆን የሀገር ሽማግሌዎች ኃላፊነታችንን መወጣት አለብን ብለዋል፡፡