የሀገር ውስጥ ዜና

በአዲስ አበባ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ እርምጃ የተወሰደባቸው ተቋማት 767 ደረሱ

By Tibebu Kebede

March 20, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ 767 የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ መወሰዱን የከተማ አስተዳደሩ ንግድ ቢሮ ገለፀ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮሮና ቫይረስ በከተማዋ መታዩቱን ተከትሎ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ እና የአቅርቦት ችግር እንዳይፈጠር ግብረ ሃይል በማቋቋም የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ቁጥጥር እያደረገ ይገኛል።