አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ከግሎባል አሊያንስ ቫክሲን ኢኒሼቲቭ ዋና ስራ አስኪያጅ ዶክተር ሲዝ በርክሌይ ጋር በክትባት አገልግሎት እና ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ፡፡
በውይይታቸውም በዋናነት ስላልተከተቡ ሕጻናት (ዜሮ ዶዝ)፣ በመጪው ጊዜ ስለሚካሄደው የኩፍኝ ክትባት ዘመቻ፣ የመረጃ አያያዝና ማሻሻል ሥራ እንዲሁም የኮቪድ ክትባት ስርጭት እና ስለሂዩማን ፓፒሎማ ቫይረስ ክትባት መክረዋል፡፡