Fana: At a Speed of Life!

በሰሜን ሸዋ ዞን አራት ወረዳዎች የማሽላ ጢንዚዛ ተከሰተ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አራት ወረዳዎች የማሽላ ጢንዚዛ መከሰቱን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

እስካሁን 1 ሺህ 21 ሔክታር የማሽላ ሰብል ላይ ጢንዝዛ የተከሰተ ሲሆን÷ 966 ሔክታሩን በባህላዊ መንገድ ቀሪውን 55 ሔክታር ደግሞ በኬሚካል የመከላከል ሥራ መሠራቱ ተገልጿል፡፡

በመምሪያው የሰብል ልማት ቡድን መሪ አበበ ጌታቸው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ በአንኮበር፣ ጣርማበር፣ ቀወት እና በረኸት ወረዳዎች የማሽላ ጢንዚዛ ተከስቷል፡፡

የቀበሌና የወረዳ ባለሙያዎች ጢንዚዛው በሰብሉ ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ÷ በባህላዊ ዘዴ በመልቀም፣ ማሽላውን በማወዛወዝና ጭስ በማጨስ እንዲሁም በኬሚካል የመከላከል ሥራ እየተሠራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

ጢንዚዛው ወደ ሌሎች አካባቢዎች ሊስፋፋ እንደሚችል ትንበያ መኖሩን ጠቁመው÷ ወደ አጎራባች ወረዳዎች እንዳይዛመት ሁሉም አርሶአደርና ድጋፍ ሰጪ ባለሙያ የመከላከል ሥራው ላይ እንዲረባረብ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በሳምራዊት የስጋት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.