ኮሮናቫይረስ

የተለያዩ ሆስፒታሎች የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ጠያቂ እንዳይገባ ከለከሉ

By Tibebu Kebede

March 20, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የተለያዩ ሆስፒታሎች የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ለመግታት እና የታካሚዎችን ደህንነት ለመጠበቅ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ላይ ይገኛሉ።

ለአብነትም የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ የተገልጋዮችን ደህንነት ለመጠበቅ በአገልግሎታችን አሠጣጥ ላይ ለውጦች ለተወሰነ ጊዜ ማድረጉን በፌስቡክ ገፁ ባወጣው መረጃ አስታውቋል።