የሀገር ውስጥ ዜና

ወደፊትለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ላይ አፋጣኝ ሥራ ሊሠራ እንደሚገባ አቶ አወል አርባ አሳሰቡ

By ዮሐንስ ደርበው

October 05, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፋር ክልል ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ላይ የተሻለ አፋጣኝ የመከላከል ሥራ ሊሠራ እንደሚገባ የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ አሳሰቡ፡፡

በአፋር ክልል በጎርፍ የሚከሰቱ ጉዳቶችን ለመቆጣጠር እየተሠሩ በሚገኙ ሥራዎች ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተወያይተዋል፡፡