ወልቂጤ ከተማ እና ኢትዮጵያ መድን ድል ቀንቷቸዋል
አዲስ አበባ ፣ መስከረም 25 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሁለት ጨዋታዎችን አስተናግዷል።
ከምሳ በኋላ በተካሄደው የመጀመሪያ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ በአዲሱ የወውድድር አመት ሁለተኛ ድሉን አስመዝግቧል፡፡
ክትፎዎቹ ባህርዳር ከተማን በተመስገን በጅሮንድ ድንቅ ግብ 1 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡
10 ሰአት ላይ በተካሄደውና ሰባት ጎሎች በተቆጠሩበት ጨዋታ ደግሞ ኢትዮጵያ መድን አርባምንጭ ከተማን 4 ለ 3 አሸንፏል።
በጨዋታው አሸናፊ ፊዳ እና ተመስገን ደረሰ (2) ለወላይታ ዲቻ ሲያስቆጥሩ፥ ብሩክ ሙሉጌታ፣ ኪቲካ ጅማ፣ አስጨናቂ ፀጋዬ እና ኢዮብ ገብረማርያም ለመድን የድል ጎሎቹን አስቆጥረዋል።