በአዲስ አበባ ከ7 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ሁለት ሜጋ ፕሮጀክቶችን ግንባታ ለማካሄድ ስምምነት ተፈረመ
ግንባታው፥ 200 ህሙማንን የሚያስተናግዱ አልጋዎች፣ 27 የድንገተኛ ህክምና መስጫ ክፍሎች እንዲሁም የቀዶ ጥገናና የፊዚዮቴራፒ ህክምናዎችን ጨምሮ የስብሰባ አዳራሾችን ያካተተ መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው በኩል አስታውቀዋል።
ፕሮጀክቶቹ ኦቪድ ግሩፕ እና በተስፋዬ ኃይሌ ኮንስትራክሽን ኩባንያዎች ይገነባሉም ተብሏል።
የፕሮጀክቶቹን ግንባታ በታቀደው ጊዜ ገደብ በፍጥነትና በጥራት በማጠናቀቅ ለሕዝብ ጥቅም እንዲውሉ ከንቲባ አዳነች አሳስበዋል።