የሀገር ውስጥ ዜና

የአማራን ሕዝብ ማዕከል አድርገው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ለመሥራት ስምምነት ላይ ደረሱ

By Tibebu Kebede

November 04, 2019

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአማራን ሕዝብ ማዕከል አድርገው የሚንቀሳቀሱት አዴፓ፣ አብን እና የአምስቱ ፖለቲካ ፓርቲዎችን ጥምረት የያዘው የአማራ ድርጅት በጋራ ለመሥራት ስምምነት ላይ ደረሱ፡፡

በአማራ ምሁራን መማክርት ጉባዔ አዘጋጅነት በአማራ ክልል እና በአገራዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያተኮረ ውይይት በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡