Fana: At a Speed of Life!

ቤላሩስ የኒውክሌር የጦር መሳሪያ ጥቃት እንደሚያሰጋት አስታወቀች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አሜሪካ በፖላንድ ያላት የአቶሚክ መሳሪያ ለኒውክሌር መሳሪያ ሊያጋልጠኝ ይችላል ስትል ቤላሩስ ገለጸች።

ፕሬዚዳንት አሌክሳንደር ሉካሸንኮ ፖላንድ በቤላሩስ ላይ የኒውክሌር ጥቃት ልታደርስ የምትችልበት እድል ሰፊ ነው በማለት ስጋታቸውን ገልጸዋል።

ቤላሩስ የኒውክሌር የጦር መሳሪያ ስሌሌላት አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፥ በጉዳዩ ላይ ከክሬምሊን እንወያያለን ብለዋል።

ፖላንድ እና ዋሺንግተን የኒውክሌር መሳሪያን መጋራት በሚችሉበት ዙሪያ በመምከር፥ ፖላንድ አሜሪካ የኒውክሌር መሳሪያዎቿን ማስቀመጥ እንድትችል ይሁንታ መስጠቷን ተከትሎ ነው ፕሬዚዳንቱ ስጋታቸውን የገለጹት።

አሜሪካ በበኩሏ ኔቶን ከፈረንጆቹ 1997 በኋላ በተቀላቀሉ አባል ሀገራት ግዛት የኒውክሌር ጦር መሳሪያ የመትከል ዕቅድ እንደሌላት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ቬዳንት ፓተል መግለጻቸውን አር ቲ ዘግቧል።

አሜሪካ የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎቿን በቤልጂየም፣ ጀርመን፣ ጣሊያን፣ ኔዘርላንድስ እና ቱርክ ውስጥ የተከለች ሲሆን፥ ሩሲያ እነዚህ የጦር መሳሪያዎች ወደ አሜሪካ እንዲመለሱ ብትጠይቅም አሜሪካ እና ኔቶ ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.