Fana: At a Speed of Life!

በሴካፋ ከ17 ዓመት በታች የእግር ኳስ ውድድር ደቡብ ሱዳን ወደ ግማሽ ፍጻሜ አለፈች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበራት (ሴካፋ) ደቡብ ሱዳን ወደ ግማሽ ፍጻሜ ማለፏን አረጋግጣለች።

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም እየተከናወነ የሚገኘውና ሰባተኛ ቀኑን በያዘው ውድድር ÷ ዛሬ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች ተካሄደዋል።

በምድብ ሁለት ደቡብ ሱዳንና ብሩንዲ ያደረጉት ጨዋታ 1 ለ 1 ተጠናቋል።

ውጤቱንም ተከትሎ ደቡብ ሱዳን ከምድቧ ዩጋንዳን ተከትላ ወደ ግማሽ ፍጻሜው አልፋለች።

በምድብ አንድ በተደረገው ጨዋታ ታንዛኒያ ሶማሊያን 2 ለ 1 ስታሸንፍ÷በዚሁ ምድብ ሁለቱ አገራት ቀድመው ለግማሽ ፍጻሜ ማለፋቸው ይታወቃል።

በምድብ ሁለት አስተናጋጅ ሀገር ኢትዮጵያ ሁለት ጨዋታ ተሸንፋ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍ አልቻለችም።

በግማሽ ፍጻሜው ዩጋንዳ ከሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን ከታንዛንያ ጥቅምት 2 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚካሄድ ኢዜአ ዘግቧል፡፡

የሴካፋ የእግር ኳስ ውድድር እስከ ጥቅምት 5 ቀን 2015 ዓ.ም ይቆያል።

በውድድሩ አንደኛ እና ሁለተኛ የሚወጡ ሀገራት በመጋቢት ወር 2015 ዓ.ም በአልጄሪያ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ከ17 ዓመት በታች የእግር ኳስ ውድድር ዞኑን ወክለው ይሳተፋሉ።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.