የፌዴሬሽን ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ስብሰባውን ማካሄድ ጀመረ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌዴሬሽን ምክር ቤት 6ኛ የፓርላማ ዘመን፣ 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን፣ 1ኛ መደበኛ ስብሰባውን ማካሄድ ጀምሯል፡፡
ምክር ቤቱ ስድስተኛ የፓርላማ ዘመን 2ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ የእለቱን የመወያያ አጀንዳዎች በማጽደቅ ውይይቱን ቀጥሏል፡፡
በቀረቡት አጀንዳዎች ላይ በዝርዝር ተወያይቶ እንደሚያጸድቅም ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።