የሀገር ውስጥ ዜና

ቤተክርስቲያኗ መንፈሣዊ የስብከተ ወንጌል ጉባኤያትና የመንፈሳዊ ጉዞ መርሐ ግብሮች ለጥቂት ቀናት እንዲቆሙ ውሳኔ አሳለፈች

By Tibebu Kebede

March 21, 2020

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 12 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንፈሣዊ የስብከተ ወንጌል ጉባኤያትና የመንፈሳዊ ጉዞ መርሐ ግብሮች ለጥቂት ቀናት እንዲቆሙ ውሳኔ አሳለፈች።

በብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊና የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ቋሚ ሲኖዶስ ያሳለፈውን ውሳኔ በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል።