የ12ኛ ክፍል የ2014 ዓ.ም የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ተጠናቀቀ
የዩኒቨርሲቲውን ግቢ ሳይለቁ ቀጣይ ፈተናዎችን የወሰዱና ያለፍላጎታቸው አንድ ፈተና ያመለጣቸው ተፈታኞችም በሚቀጥለው ዙር ፈተናው እንደሚሰጣቸው ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
ፈተናውን በፍላጎታቸው ጥለው የወጡ ተፈታኞችን ግን ዳግም የሚሰጠው ፈተና እንደማይመለከታቸው ተጠቁሟል፡፡
በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረው አደጋ ፈተና ያልወሰዱትም በቀጣይ ይፈተናሉ ተብሏል።
በሁለተኛው ምዕራፍ ለተፈጥሮ ሣይንስ የትምህርት መስክ ተፈታኞች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ጥቅምት 8 ቀን ፣ 2015 መሰጠት እንደሚጀምር ታውቋል።