የሀገር ውስጥ ዜና

በኦሮሚያ ክልል ባለፉት አራት ዓመታት 4 ቢሊየን የቡና ችግኞች ተተክለዋል – አቶ ሽመልስ አብዲሳ

By ዮሐንስ ደርበው

October 13, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ባለፉት አራት ዓመታት በቡና ልማት የተከናወነው ስራ የምርቱን የወጪ ንግድ መጠን እንዳሳደገው የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ትስሰር ገፃቸው ላይ እንዳስታወቁት፥ ከአራት ዓመት በፊት የክልሉ መንግስት የነቀምቴ የቡና ስምምነት የተሰኘ ተነሳሽነትን በማፅደቅ ወደ ስራ ገብቷል።