Fana: At a Speed of Life!

የሶማሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዜ አብዲ አዲስ አበባ ገቡ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዜ አብዲ የተመራው የሶማሊያ ፌደራላዊ ሪፐብሊክ መንግሥት ከፍተኛ ልዑክ አዲስ አበባ ገቡ።

ለልዑኩ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ፣ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሃመድና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባህርዳር ከተማ በሚካሄደው የጣና ፎረም ላይ ይካፈላሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

የጣና ፎረም 10ኛ ዓመት ጉባዔ ከነገ ጥቅምት 4 እስከ 6/2015 በባህር ዳር ከተማ ይካሄዳል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.