አዲስ አበባ፣መጋቢት 13፣2012(ኤፍ.ቢ.ሲ)ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ኮሮና ቫይረስን አስመልክተው ከጣሊያኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ጁሴፔ ኮንቴን ጋር ተወያይተዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ በትናንት ምሽት ውይይታቸው ÷በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ከጣሊያን ሕዝብ ጎን ነን ብለዋል፡፡
አያይዘውም የዓለም ማኅበረሰብ እንደ መሆናችን፣ ይህንን ሁኔታ በመተባበር እና በአንድነት ድል እንነሣዋለን ማለታቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የፌስ ቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።