Fana: At a Speed of Life!

የመከላከያ ሠራዊት አባላት የሰንደቅ ዓላማ ቀንን አከበሩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የመከላከያ ሠራዊት አባላት 15ኛውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን አከበሩ።

ቀኑ ጦር ሃይሎች በሚገኘው የመከላከያ ጠቅላይ መምሪያ ግቢ የተከበረ ሲሆን ፥ የመከላከያ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ማርታ ሊዊጂም ፣ ከፍተኛ መኮንኖችና የሠራዊቱ አባላት ተገኝተዋል።

የመከላከያ ሚኒስቴር ትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌተናል ጄነራል ይመር መኮንን በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፥ ጥንት አባቶች በትውልድ ቅበብሎሽ በከፈሉት መስዋዕትነት ሰንደቅ ዓላማችንን ከፍ አድርገው አቆይተዋል።

የአሁኑ ትውልድም የሀገር ዳር ድንበርን በማስከበር ረገድ አኩሪ ስራ ማከናወኑንም ነው የተናገሩት።

በቀጣይም አስፈላጊውን ሁሉ መስዋዕትነት ለመክፈል ሠራዊቱ ዝግጁ ነው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.