አዲስ አበባ “በትምህርት ቤቶች የምገባ ፕሮግራም” ከ133 ከተሞች ጋር ተወዳድራ አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲስ አበባ “በትምህርት ቤቶች የምገባ ፕሮግራም” ምርጥ ተሞክሮ በ8ኛው የሚላን የከተማ ምግብ ፖሊስ ስምምነት ግሎባል ፎረም ዘላቂ አመጋገብ እና ሥነ ምግብ ዘርፍ አሸንፋለች፡፡
አዲስ አበባ ይህንን ሽልማት ያሸነፈችው በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ133 ከተሞች ጋር ተወዳድራ መሆኑ ታውቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ሽልማቱን በተቀበሉበት ወቅት÷ በኢትዮጵያ ቅድሚያ ለሰው የሚሰጥ ፖሊሲ በማውጣት እየተከናወነ ስላለው ሰው ተኮር ተግባራት ከሚላን የከተማ ምግብ ፖሊስ ስምምነት ፈራሚ ከተሞች ለመጡ ከንቲባዎች እና ተሳታፊዎች ልምድ አካፍለዋል።
በከንቲባ አዳነች አቤቤ የተመራ ልዑክ÷ “Food to Feed the Climate Justice: urban food solutions for a fairer world” በሚል መሪ ሐሳብ በብራዚል ሪዮ ዲጄኔሮ እየተካሄደ በሚገኘው 8ኛው የሚላን የከተማ ምግብ ፖሊስ ስምምነት ግሎባል ፎረም ላይ እየተሳተፈ ነው፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!