በኦሮሚያ ክልል ለተጎዱ ወገኖችና ተቋማት የሚውል የ1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ድጋፍ ተደረገ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ለኦሮሚያ ክልል 1ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ድጋፍ አደረገ።
የተደረገው ድጋፍ በክልሉ በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖችና ለወደሙ ተቋማት የሚውል መሆኑ ተገልጿል፡፡
ድጋፉን ያስረከቡት የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ኢ/ር ጫልቱ ሳኒ ሲሆኑ ፥ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ መረከባቸውን ከክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!