Fana: At a Speed of Life!

የአዋሽ መልካሳ የኬሚካል ፋብሪካን የማምረት አቅም ለማሳደግ እንሰራለን – ኢ/ር ታከለ ዑማ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዋሽ መልካሳ የኬሚካል ፋብሪካ ያሉበትን ችግሮች በመፍታት የማምረት አቅሙን ለማሳደግ እንሰራለን ሲሉ የማዕድን ሚኒስትር ኢ/ር ታከለ ዑማ ገለጹ፡፡

ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ፥ ለሀገራት ኢንደስትሪ እድገት መሰረት የሆነውን የሰልፈሪክ አሲድን በሚያመርተው የአዋሽ መልካሳ የኬሚካል ፉብሪካ መጎብኘታቸውን ገልጸዋል፡፡

ፋብሪካው በተለይም ማዳበሪያን በሀገር ውስጥ ለማምረት እንደ ግብአት ልናውለው የምንችለውን ሰልፈሪክ አሲድና ለውሀ ማጣሪያ የሚውለውን አልሙኒየም ሰልፌት በዋነኝነት እያመረተ ይገኛልም ነው ያሉት።

ሆኖም ፋብሪካው ባለበት የግብአት ችግር ምክንያት ማምረት በሚችለው ልክ እያመረተ እንዳልሆነ ገልጸዋል፡፡

ምርቱም በግብርናውና በኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚኖረው ሚና ሲታይ የፋብሪካውን መደገፍ ትልቁ አማራጭ እንደሚሆንም ነው የጠቆሙት፡፡

ሚኒስትሩ አክለውም ፥ በቀጣይም ፋብሪካው ያሉበት ችግሮች ተፈተው የማምረት አቅሙን እንዲያሳድግ እንደሚሰሩም ተናግረዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.