የሀገር ውስጥ ዜና

ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ ረቂቅ አዋጅን ጨምሮ 3 ረቂቅ አዋጆችን ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መራ

By ዮሐንስ ደርበው

October 20, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 10፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ ረቂቅ አዋጅን ጨምሮ ሦስት ረቂቅ አዋጆችን ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መርቷል፡፡

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ተካሂዷል፡፡