Fana: At a Speed of Life!

አምባሳደር ዘነበ ከበደ ከተመድ የሰብአዊ መብቶች ቢሮ ከፍተኛ ኮሚሽነር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጄኔቫ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ዘነበ ከበደ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ቢሮ ከፍተኛ ኮሚሽነር ቮልከር ተርክ ጋር ውይይት አደረጉ።

አምባሳደር ዘነበ ከኮሚሽነር ተርክ ጋር በነበራቸው ቆይታ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ሁኔታ በተመለከተ ገለጻ ማድረጋቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ሁለቱ አካላት ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን በጄኔቫ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ መረጃ ያመለክታል።

ከዚህ ቀደም በተመድ የስደተኞች አገልግሎት ረዳት ከፍተኛ ኮሚሽነር በመሆን ያገለገሉት ኦስትሪያዊ የሕግ ባለሙያ ቮልከር ተርክ በሚሼል ባቺሌት ቦታ መተካታቸው ይታወቃል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.