Fana: At a Speed of Life!

ኢራን 40 የጋዝ ተርባይኖች ለሩሲያ ልትሸጥ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢራን በራስ ዐቅም ያመረተቻቸውን 40 የጋዝ ተርባይኖች ለሩሲያ ለመሸጥ የኮንትራት ስምምነት መፈራረሟ ተገለጸ፡፡

አሁን ላይ ኢራን 85 በመቶ የሚሆነውን ከጋዝ አቅርቦት ጋር የተያያዙ መሳሪያዎች እና ቁሶች በሀገር ውስጥ የማምረት ዐቅም እንዳላት ይነገራል።

ምንም እንኳን አሜሪካ በኢራን ላይ ጠንካራ ነው ያለችውን ማዕቀብ ብትጥልም ኢራን ግን የጋዝ ምርቷን በእጥፍ ማሳደግ እንደቻለች ነው የኢራን ጋዝ ኢንጂነሪንግ እና ልማት ኩባንያ ኃላፊ ሬዛ ኖሻዲ የተናገሩት።

ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኢራን እና ሩሲያ ትብብራቸውን በተለያዩ መስኮች እያሳደጉ መምጣታቸውን መረጃዎች ያመላክታሉ።

በፈረንጆቹ ሐምሌ ወር ላይ ሩሲያ በኢራን የነዳጅ ኢንዱስትሪ ላይ መዋዕለ-ነዋይ ለማፍሰስ እስከ 40 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የሚደርስ የመግባቢያ ሥምምነት መፈራረማቸውን ሺንዋ “ሻና” የተሰኘውን የኢራን የነዳጅ ሚኒስቴር የዜና ምንጭ ጠቅሶ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.