Fana: At a Speed of Life!

በፕሪሚየር ሊጉ የተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀቁ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ዛሬ የተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቅቀዋል፡፡

ቀደም ሲል በምሳ ሰዓት ጨዋታቸውን ያደረጉት ሀዋሳ ከተማ እና ድሬዳዋ 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል፡፡

የሀዋሳ ከተማን ግቦች ላውረንስ ላርቴ እና አሊ ሱለይማን ሲያሰቆጥሩ÷ ቢኒያም ጌታቸው ደግሞ  የድሬዳዋን  ሁለቱን ግቦች በስሙ አስቆጥሯል፡፡

10 ሰዓት የተደረገው የኢትዮ ኤሌክትሪክ እና የአዳማ ከተማ ጨዋታ በተመሳሳይ 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል፡፡

ሄኖክ ኤለ እና አብነት ደምሴ የኢትዮ ኤሌክትሪክን ሁለት ግቦች ሲያስቆጥሩ÷  መሱድ መሀመድ እና አብዲሳ ጀማል ደግሞ የአዳማ ከተማን ግቦች አስቆጥረዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.