የሀገር ውስጥ ዜና

በየካ ክ/ከተማ ከ182 ሺህ 400 ብር በላይ ሐሰተኛ ገንዘብ ተያዘ

By ዮሐንስ ደርበው

October 26, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 አስተዳደር ልዩ ስሙ 02 አካባቢ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ182 ሺህ 400 ብር በላይ ሐሰተኛ ገንዘብ ተያዘ፡፡

ከተያዘው ሐሰተኛ ገንዘብ ውስጥም ባለ 200 የብር ኖት 150 ሺህ 400 ብር፣ ባለ 100 የብር ኖት ደግሞ 32 ሺህ ብር እንደሚገኝበት ተጠቁሟል፡፡