የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር የሳይንስ ሙዚየምን ጎበኙ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ16ኛው የኢትዮ-ጂቡቲ የጋራ የሚኒስትሮች ስብሰባ የተሳተፉት የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር መሃመድ አሊ ዩሱፍ ሳይንስ ሙዚየምን ጎበኙ።
በኢትዮጵያ እና ጂቡቲ መካከል ያለው ጠንካራ እና ታሪካዊ ግንኙነት በቴክኖሎጂና በሳይበር ደህንነት መስክም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ሚኒስትሩ መሃመድ አሊ ዩሱፍ በጉብኝታቸው ወቅት ተናግረዋል፡፡
ሚኒስትሩ በሳይንስ ሙዚየም ለእይታ የቀረቡ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እና የሌሎች ተቋማትን ምርትና አገልግሎቶችን መመልከታቸውንም ከኢመደአ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!