Fana: At a Speed of Life!

ከሰሜን ወሎና አካባቢው በአሸባሪው ህወሓት ተፈናቅለው የነበሩ ወገኖች ወደ ቀያቸው እየተመለሱ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከአላማጣ፣ ቆቦ፣ ዋጃ እና ባላ እንዲሁም ከሌሎች አካባቢዎች በአሸባሪው ህወሓት ተፈናቅለው በጃራ መጠለያ ካምፕ የነበሩ 30 ሺህ 400 ወገኖች ወደ ቀያቸው መመለስ ጀምረዋል፡፡

ሃብትና ንብረታቸው በሽብር ቡድኑ በመዘረፉ መንግሥት ቀጣይነት ያለው ድጋፍ እንዲያደርግላቸውም ጠይቀዋል።

የሰሜን ወሎ ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽ/ቤት ኃላፊ ዓለሙ ይመር ÷ ተፈናቃዮችን መልሶ ለማቋቋም የተራድዖ ድርጅቶች ጭምር ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡

የአማራ ክልል መንግሥት የአካባቢውን ሰላም በመጠበቅ የመልሶ ማቋቋም ሥራዎችን በትኩረት እየሠራ መሆኑን የሰሜን ወሎ ዞን ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.