የሀገር ውስጥ ዜና

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የሠላም ንግግሩ ውጤት ኢትዮጵያን ወደፊት ለማራመድ ትልቅ ፋይዳ ያለው መሆኑን ገለጹ

By ዮሐንስ ደርበው

November 02, 2022

 

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ ለአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን እና ለአፍሪካ ኅብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ለቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ፣ ከሠላም አባላቱ ጋር እንዲሁም በሠላም ንግግሩ ላይ ለተሳተፉ ከፍተኛ ተወካዮች ፣ ለቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና ለቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ፉሙዚሌ ማላምቦ ፣ እንዲሁም የአፍሪካ ኅብረት መርኅ የሆነውን “ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ ፍትሔዎች” የሚለውን አቋም ለመሩት የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማትን በኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት ሥም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።