ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ ለአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን እና ለአፍሪካ ኅብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ለቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ፣ ከሠላም አባላቱ ጋር እንዲሁም በሠላም ንግግሩ ላይ ለተሳተፉ ከፍተኛ ተወካዮች ፣ ለቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና ለቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ፉሙዚሌ ማላምቦ ፣ እንዲሁም የአፍሪካ ኅብረት መርኅ የሆነውን “ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ ፍትሔዎች” የሚለውን አቋም ለመሩት የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማትን በኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት ሥም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።