Fana: At a Speed of Life!

በአፍሪካ ሕብረት አማካኝነት ለተደረሰው የሰላም ስምምነት ስኬት አሜሪካ ድጋፏን ትቀጥላለች- አንቶኒ ብሊንከን

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ ሕብረት አማካኝነት ለተደረሰው የሰላም ስምምነት ስኬት አሜሪካ ድጋፏን ትቀጥላለች ሲሉ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ገለጹ፡፡

በፕሪቶሪያ ሲካሔድ የቆየው የኢፌዴሪ መንግስትና ህወሓት የሰላም ውይይት በስኬት መጠናቀቁንም አድንቀዋል፡፡

አንቶኒ ብሊንከን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ ደቡብ አፍሪካ ከአፍሪካ ሕብረት ጋር በመተባበር መድረኩን በማዘጋጀቷ አመስግነዋል፡፡

የሰብዓዊ እርዳታና መልሶ መቋቋም ሥራን በተመለከተም አሜሪካ ከአፍሪካ ሕብረት ጎን በመሆን ድጋፏን እንደምታጠናክር አረጋግጠዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.