በፕሪሚየር ሊጉ ወላይታ ድቻ እና ወልቂጤ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ6ኛው ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ድሬዳዋ ላይ ሁለት ጨዋታዎች ተካሂደዋል፡፡
10 ሰዓት ላይ ወላይታ ድቻ እና መቻል ባደረጉት ጨዋታ ወላይታ ድቻ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የወላይታ ድቻን የማሸነፊያ ግብ ቃልኪዳን ዘላለም በ31ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡
ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ደግሞ ወልቂጤ ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የወልቂጤ ከተማን ማሸነፊያ ግቦች ጌታነህ ከበደ በ21ኛው እና 52 ኛው ደቂቃ ላይ ሲያሥቆጥር÷ ለኢትዮ ኤሌክትሪክ ደግሞ ታፈሰ ሰርካ በተጨማሪ ደቂቃ አስቆጥሯል፡፡