የሀገር ውስጥ ዜና

ለኮቪድ 19 ድንገተኛ ሁኔታ ዝግጅት የሚውል ገንዘብና ሌሎች አቅርቦቶችን የሚያሰባስብ ብሔራዊ ኮሚቴ ተቋቋመ

By Tibebu Kebede

March 25, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 16፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለኮቪድ 19 ድንገተኛ ሁኔታ ዝግጅት የሚውል ገንዘብ እና ሌሎች አቅርቦቶችን የሚያሰባስብ ብሔራዊ የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ አቋቁመዋል።

መንግሥት ከፍ ያለ በጀት መድቦ አስቸጋሪ ነገሮች ሲከሰቱ ለመቋቋም የሚያስችሉ ግብአቶችን በማሰባሰብ ላይ ይገኛል ተብሏል።