Fana: At a Speed of Life!

በምሥራቅ ሸዋ ዞን ከ200 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበጋ ስንዴ ለማልማት ታቅዷል

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ከ200 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበጋ ስንዴ ለማልማት ማቀዱን የዞኑ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ሃላፊ አቶ መስፍን ተሾመ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በነበራቸው ቆይታ÷በተያዘው ዓመት የበጋ ወራት ኢትዮጵያ የያዘችውን ስንዴ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ የማቅረብ ዕቅድ ለማሳካት እየተሰራ ነው ብለዋል።

አቶ መስፍን ተሾመ ዕቅዱን ከግብ ለማድረስም በአርሶ አደሩ የሚነሱ የውሃ መሳቢያ ሞተር እና ሌሎች የግብዓት አቅርቦት ችግሮችን የመፍታት ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል፡፡

ከ2 ሺህ በላይ የሞተርፓምፖች ለአርሶ አደሩ ተገዝተው የማሰራጨት ሥራ መከናወኑም ነው የተጠቆሙት፡፡

በቀጣይም ለሥርጭት የተዘጋጁ ከ200 በላይ ትልልቅ የውሃ መሳቢያ ጀነሬተሮች መዘጋጀታቸውንም የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባቡ ዋቆ ተናግረዋል።

አርሶ አደሮች በበኩላቸው ÷ የበጋ ስንዴን በስፋት ለማምረት በመንግስት በኩል የሚቀርቡ ግብዓቶችን በወቅቱ ለመጠቀም ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በይስማው አደራው

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.