አዲስ አበባ ፣መጋቢት 17፣2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ህዝብ ክልላዊ መንግስት የመስተዳድር ምክር ቤት የኮረና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል።
ምክር ቤቱ ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፥ ሁሉም የመንግስት ተቋማት ለአካል ጉዳተኛ፣ ዕድሜያቸው 50 ዓመትና በላይ ለሆኑ፣ ለነፍሰ ጡርና አጥቢ እናቶች፣ ከቫይረሱ ጋር ተዳብለው ጉዳት የሚያስከትል ህመም ላለባቸው ሰራተኞች እንዲሁም በየመኖሪያቸው ገጠር ሆኖ ከተማ ባለ የመንግስት ተቋም ለሚሰሩ ሰራተኞች ፍቃድ በመስጠት ቤታቸው እንዲቆዩ ማድረግ እንዳለባቸው አስታውቋል።