የኢንቨስትመንት አስፈፃሚ አካላት የጋራ የምክክር መድረክ በጎንደር ከተማ እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌዴራል የክልል እና የከተማ አስተዳደር የኢንቨስትመንት አስፈፃሚ አካላት የጋራ የምክክር መድረክ በጎንደር ከተማ መካሄድ ጀምሯል፡፡
የክልል እና የከተማ አስተዳደር ኮሚሽነሮች እና የቢሮ ሃላፊዎች በ2015 ዓ.ም ሩብ በጀት ዓመት በኢንቨስትመንት ስበት እና በድጋፍ እና ክትትል የአፈፃፀም ሪፖርት እንደሚቀርቡ ከኢንቨስትመንት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
በምክክር መድረኩ ቀጣይ የጋራ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡