አዲስ አበባ ፣መጋቢት 17፣2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት በውሃ አቅርቦት እና ሳኒቴሽን ዙሪያ የሚሠራ ኮሚቴ መቋቋሙን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታውቋል።
የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት በሚደረገው ጥረት ዙሪያ በዘርፉ የተሰማሩና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በሚሳተፉበትና የበኩላቸውን ድጋፍ በሚያደርጉበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተደርጓል።