የህክምና ቁሳቁሶችን የጫኑ ሁለት የጭነት ተሽከርካሪዎች መቀሌ ደረሱ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአስቸኳይ ጊዜ እና የመጀመሪያ የህክምና እርዳታ ለመስጠት የሚያስችሉ የህክምና ቁሳቁሶችን የያዙ ሁለት ተሽከርካሪዎች መቀሌ መድረሳቸውን ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ማህበር አስታወቀ፡፡
መቀሌ የደረሱት መድሃኒቶች አስቸኳይ የህክምና ድጋፍ ለሚሹ ሰዎች እንደሚሆኑም ማህበሩ አስታውቋል።
በሚቀጥሉት ቀናቶችም ሌሎች ተጨማሪ ድጋፎች ወደ ክልሉ እንደሚገቡም አመልክቷል።