Fana: At a Speed of Life!

ሊግ ኩባንያው የቴሌቪዥን መብት የመጀመሪያ ክፍያን ለክለቦች አስረከበ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማኅበር የ2015 ዓ.ም የቴሌቪዥን መብት የመጀመሪያ ክፍያን ለክለቦች መፈጸሙን አስታውቋል፡፡

በዚህ መሰረትም የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ታሳታፊ 16 ክለቦች እያንዳንዳቸው 2 ነጥብ 1 ሚሊየን ብር ከሊግ ኩባንያው ማግኘታቸው ተመላክቷል፡፡

የማኅበሩ ሥራ አስኪያጅ አቶ ክፍሌ ሰይፈ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ ለኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች በአጠቃላይ ከ33 ሚሊየን ብር በላይ ክፍያ በሊግ ኩባንያው ተፈጽሟል፡፡

ክለቦቹ ካገኙት የቴሌቪዥን የመብት ሽያጭ ክፍያ ለኮሚሽነሮችና ዳኞች ክፍያ መፈጸማቸውንም ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።

በወርቅነህ ጋሻሁን

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.