Fana: At a Speed of Life!

በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለማቋቋም እየሰሩ መሆኑን የደቡብ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ገለፁ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለማቋቋም በትኩረት እየሰሩ መሆኑን የደቡብ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች አስታወቁ።

የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ርስቱ ይርዳ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ቆይታ ÷ በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለማቋቋም የሚያግዙ የሃብት ማሰባሰብ ስራዎች ጀምረናል ብለዋል።

ለዚሁ ስራም በክልሉ ግብረ ሃይል መቋቋሙን የተናገሩት ርዕሰ መስተዳድሩ÷ በዚህም እስካሁን 52 ሚሊየን ብር መሰብሰቡን ጠቁመዋል።

የአይነት ድጋፎችንም በጦርነቱ ለተጎዱ አካባቢዎች ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን ነው አቶ ርስቱ የተናገሩት።

እንዲሁም በጦርነቱ ለተለያዩ ስነ-ልቦናዊ እና ተያያዥ ችግሮች የተጋለጡ ወገኖች የሚያስፈልጋቸውን ሙያዊ እገዛ ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነም አንስተዋል፡፡

የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በበኩላቸው÷ በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን በሁሉም ዘርፍ መልሶ የማቋቋም ስራ ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሮቹ በጦርነቱ ጉዳት ለደረሰባቸው አካባቢዎች የሚያስፈልጉ ድጋፎችን ከማቅረብ ረገድ የሚያከናውኑትን ተግባር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል፡፡

በዙፋን ካሳሁን

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.