የሀገር ውስጥ ዜና

ክልሎች የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አድርገዋል

By Tibebu Kebede

March 28, 2020

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 19 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ ምክትል ርዕሳነ መሥተዳድሮች እና ከሁለቱ ከተማ መስተዳድሮች ከንቲባዎች ጋር በኮሮና ቫይረስ የመከላከል ተግባራት ዙሪያ ተወያይተዋል።

በዚህ ወቅትም ሁሉም ክልሎች የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል አስፈላጊ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን አስታውቀዋል።