Soccer Football - FIFA World Cup Qatar 2022 - Group G - Brazil v Switzerland - Stadium 974, Doha, Qatar - November 28, 2022 Brazil's Casemiro celebrates scoring their first goal with Vinicius Junior REUTERS/Marko Djurica

ስፓርት

 ብራዚል ጥሎ ማለፉን መቀላቀሏን አረጋገጠች

By Melaku Gedif

November 28, 2022

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታር ዓለም ዋንጫ ብራዚል እና ስዊዘርላንድ ምሽት ላይ የምድብ ሁለት ጨዋታቸውን አካሂደዋል፡፡

በዚህም ብራዚል ስዊዘርላንድን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ በምድቡ ያላትን ነጥብ ወደ ስድስት ከፍ አድርጋለች፡፡

ውጤቱን ተከትሎም ከፈረንሳይ በመቀጠል ጥሎ ማለፉን የተቀላቀለች ሁለተኛ ሀገር መሆን ችላለች፡፡

የብራዚልን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ካሰሚሮ 83ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡