የ“አይ ኤስ” መሪ አቡ አል-ሐሰን አል-ሐሺም አል-ቁራሺ ተገደለ
አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 22 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሽብር ቡድኑ “ካሊፍ” ብሎ የሚጠራው የ “አይ ኤስ አይ ኤስ” መሪ አቡ አል-ሐሰን አል-ሐሺም አል-ቁራሺ መገደሉ ተነግሯል፡፡
አቡ አል-ሐሰን አል-ሐሺም አል-ቁራሺ በውጊያ ላይ መገደሉን የአይ ኤስ ሽብር ቡድን ምክትል መሪ ማስታወቁን አርቲ እና ሬውተርስን ጨምሮ በርካታ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል፡፡
የሽብር ቡድኑ መሪው የተገደለበትን ሁኔታ ፣ ጊዜ እና ቦታ አስመልክቶ ዝርዝር መረጃ አለመስጠቱ በዘገባው ተመላክቷል፡፡
“አይ ኤስ አይ ኤስ” ፣ ቀደም ሲል “አይ ኤስ አይ ኤል” በኢራቅ ደግሞ አልቃይዳ
በመባል የሚጠራው የሽብር ቡድን በፈረንጆቹ ሚያዚያ 2004 በአቡ ሙስዓብ አል ዛርቃዊ መመስረቱ ይነገራል፡፡