17ኛው የብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በድሬዳዋ ተከበረ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) “ኅብረብሔራዊ አንድነት ለዘላቂ ሰላም” በሚል መሪ ሐሳብ 17ተኛው የብሐር፣ ብሔረሰቦና ሕዝቦች ቀን በድሬዳዋ ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል፡፡
በአከባበሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ ዛሃራ ዑሙድ÷ በዓሉን ስናከብር የአንድነት መንፈስን የሚያሰርፁ ተግባራትን አጠናክሮ በማስቀጠል መሆን አለበት ብለዋል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ፈቲያ አደን÷ ድሬዳዋ የተለያዩ ብሔሮች ብሔረሰቦችንና ሕዝቦችን አቅፋ የምትኖር የትንሿ ኢትዮጵያ ተምሳሌት መሆኗን ገልጸዋል፡፡
ይህን ዕሴት ለማስቀጠልም ወንድማማችነትና አብሮነትን የሚያጎለብቱ ሥራዎችን መስራት ይገባል ብለዋል፡፡
በቲያ ኑሬ