የሀገር ውስጥ ዜና

ፕሬዚዳንት ሳኅለወርቅ ዘውዴ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ ጋር ተወያዩ

By Tamrat Bishaw

December 01, 2022

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሳኅለወርቅ ዘውዴ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

በውይይታቸውም በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታና በዓለም አቀፍ የጋራ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡