Fana: At a Speed of Life!

በወራቤ አንዲት እናት በአንድ ጊዜ አራት ልጆችን ተገላገሉ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በትናንትናው ዕለት በወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አንዲት እናት በአንድ ጊዜ አራት ልጆችን በሰላም ተገላግለዋል።

ወ/ሮ ነፊሳ ሸምሰዲን በስደት ከሚኖሩበት ሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ትውልድ ቀያቸው ሳንኩራ ወረዳ ዓለምገበያ ከተማ በጉዞ ላይ ሳሉ÷ በተሰማቸው ሕመም ምክንያት ወደ ወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ያቀናሉ፡፡

በሆስፒታሉ የሕክምና ባለሙያዎች በተደረገላቸው ቀዶ ጥገናም÷ ሦስት ወንድና አንዲት ሴት ልጆችን በሰላም ተገላግለዋል፡፡

ወይዘሮ ነፊሳ ቀደም ሲል በተለያየ ጊዜ የወለዷቸው ሁለት ልጆች እንዳሏቸው አስታውሰው÷ በአሁኑ ሰዓት አራት ልጆችን በአንድ ጊዜ በመውለዳቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡

የተወለዱት ሕጻናት በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙ የሆስፒታሉ መረጃ አመላክቷል፡፡

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.