Soccer Football - FIFA World Cup Qatar 2022 - Round of 16 - France v Poland - Al Thumama Stadium, Doha, Qatar - December 4, 2022 France's Olivier Giroud celebrates scoring their first goal with teammate Kylian Mbappe REUTERS/Hannah Mckay

ስፓርት

ፈረንሳይ ፖላንድን በማሸነፍ ሩብ ፍፃሜውን ተቀላቀለች

By Mikias Ayele

December 04, 2022

አዲስ አበባ፣ህዳር 25፣2015 (ኤፍ ቢሲ) በኳታር ዓለም ዋንጫ ፈረንሳይ ፖላንድን 3 ለ 1 በማሸነፍ ሩብ ፍፃሜውን ተቀላቅላለች፡፡

በአልቱማም ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የፈረንሳይን የማሸነፊያ ጎሎች ኦሊቪዬር ጂሩ እና ኬሊያን ምባፔ አስቆጥረዋል፡፡

የፖላንድን ብቸኛ ጎል ሮቤርቶ ሌቫዶቭስኪ በተጨማሪ ሰዓት በፍፁም ቅጣት ምት አስቆጥሯል፡፡

ኦሊቪዬ ጂሩ በዛሬው ጨዋታ ጎል ማስቆጠሩን ተከትሎ በ52 ጎሎች የፈረንሳይ የምንጊዜም ጎል አግቢነት ክብረወሰኑን  ከቴሪ ሄነሪ ተረክቧል፡፡

እንዲሁም ሁለት ጎሎችን ያስቆጠረው ኬሊያን ምባፔ ከ24 ዓመቱ በፊት በዓለም ዋንጫው ዘጠኝ ጎል ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች መሆን ችሏል፡፡

ከዚህ በፊት የብራዚሉ ፔሌ ከ24 ዓመት በፊት ሰባት ጎል ያስቆጥረ ብቸኛ ተጫዋች ሲሆን÷ይሄው ክብረወሰን በኬሊያን ምባፔ ተሻሽሏል፡፡