አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 21 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ)በደቡብ ክልል ከዛሬ ከቀኑ 6 ሰዓት ጀምሮ አዲስ አበባን ጨምሮ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች ወደ ወደ ደቡብ ክልል ሁሉም የህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ስምሪት እንዲቋረጥ ተወሰነ፡፡
የደቡብ ክልል የኮሮና ወረርሽኝ በሽታ መቆጣጠሪያና መከላከል ግብረ ሀይል ዛሬ በሰጠው መግለጫ ከፍተኛ አገር አቋራጭ ትራንስፖርትና ከክልል ወደ ክልል የሚደረግ አነስተኛና መለስተኛ የህዝብ ትራንስፖርት ስምሪት ላልተወሰነ ጊዜ መቋረጡን ገልጿል፡፡