የሀገር ውስጥ ዜና

አካላዊ ርቀት በግብይት ስፍራዎችና በትራንስፖርት መገልገያዎች ተግባራዊ እየተደረገ አለመሆኑ ተገለፀ

By Tibebu Kebede

March 31, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አካላዊ ርቀት በግብይት ስፍራዎች እና በትራንስፖርት መገልገያዎች ተግባራዊ እየተደረገ አለመሆኑ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ19) ለመከላከል የተቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ ገለፀ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ19) ለመከላከል ከተቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ የንዑሳን ኮሚቴ ኃላፊዎች ጋር በኢንተርኔት ውይይት ማካሄዳቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል።